ማጠቃለያ

በዚህ ዓለም ላይ የምንገኝ ሁሉ ፍፁም የሆነ ደስታን ለማግኘት ስንሻ እንገኛለን፡፡ ነገር ግን ፍፁም የሆነው ደስታ ምን እንደሆነ የተረዳንበት ደረጃ ላይ አልደረስንም፡፡ በተለያዩ ማስታወቂያዎች ላይ ብዙ ደስታን ሊሰጡ የሚችሉ ነገሮች ቀርበው ይታያሉ፡፡ ቢሆንም ግን በጣም ጥቂት የሚሆኑ ሰዎች ፍፁም በሆነ ደስታ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡ ምክንያቱም ፍፁም ደስታ የሚገኘው ከጊዜያዊ እና ከዓለማዊ ኑሮ ሳይሆን ከዚህ ዓይነቱ ኑሮ ባሻገር በመሆኑ ነው፡፡
ይህንንም የተረዱ ሰዎች በጣም ጥቂት ናቸው፡፡
በዚህም “ጉዞ ወደ ክርሽና” ተብሎ በተሰየመው መጽሀፍ ውስጥ የተገለፀው እንዴት ይህንኑ ፍፁም ደስታ ለማግኘት እንደምንችል ነው፡፡